የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በፓርቲዎች የሥነ-ምግባር አዋጅ ዙሪያ በአዲስ አበባ ከተማ በዕጩነት ለቀረቡ ተወዳዳሪዎችና ከየአካባቢው ለመጡ አባላቱ ዕሑድ የካቲት 28 ቀን 2002 ዓ.ም የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠቱን ከፓርቲው ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ።በቅሎ ቤት አካባቢ በሚገኘው የፓርቲው ጽ/ቤት አዳራሽ ውስጥ የተሰጠው ስልጠና በፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበር በወ/ሮ ሶፍያ ይልማ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የተከፈተ መሆኑ ታውቋል። ይኸው ስልጠና በፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ በአቶ ደረጀ ደበበ እና በውጭ ግንኙነት ኃላፊው በአቶ አብዱራህማን አህመዲን አማካይነት የተሰጠ መሆኑንም ከጽ/ቤቱ ያገኘነው መረጃ ጨምሮ ገልጿል።













