12 የክርክር አጀንዳዎች ተመረጡ፤ ክርክሩ የካቲት 5 ይጀምራል ተባለ
ግንቦት 15 ቀን 2002 ዓ.ም በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ በተቃዋሚ ፓርቲዎችና በኢህአዴግ መካከል የሚካሄደው ክርክርና የምረጡኝ ዘመቻ የካቲት 5 ቀን 2002 ዓ.ም እንደሚጀምር ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ።
Read more...
የኢዴፓ አጀንዳ በፓርላማ እንዳይቀርብ ኢህአዴግና ህብረት ተቃወሙከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ በመጣው የነዳጅ ዋጋና ከዚሁም ጋር ተያይዞ እየናረ በመጣው የኑሮ ውድነት ዙሪያ ፓርላማው “በተቀዋሚዎች ቀን” እንዲመክርበት ኢዴፓ አጀንዳ ማቅረቡ ይታወሳል። ይኸው አጀንዳ በምክር ቤቱ የአሰራር ደንብ መሰረት በጥር ወር የመጨረሻ ሳምንት ማክሰኞ በሚካሄደው የም/ቤቱ መደበኛ ስብሰባ እንደሚቀርብ ቀደም ሲል ቅንጅት ያቀረበው አጀንዳ በታህሳስ ወር እንዲቀርብ በተወሰነበት ወቅት ስምምነት የተደረሰበት ቢሆንም፤ ኢህአዴግና ህብረት ባቀረቡት ተቃውሞ የኢዴፓ አጀንዳ እንዳይቀርብ መደረጉን በፓርላማ የኢዴፓ ተጠሪ የሆኑት አቶ አብዱራህማን አህመዲን አስታውቀዋል። የኢዴፓ አመራር አባላት በተለያዩ የምርጫ ክልሎች በዕጩነት እየተመዘገቡ ነው፤ አቶ ልደቱ ዛሬ ተመዘገቡየኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በግንቦት ወር 2002 ዓ.ም በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ፣ ከሀገሪቱ የቆዳ ስፋት ሰባ አምስት በመቶ በሚሆነው አካባቢ ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ለማቅረብ ካለፈው ሐምሌ ወር 2001 ዓ.ም ጀምሮ ዝግጅት ሲያደርግና የማደራጀት ስራ ሲያከናውን ከርሞ ዕጩ ማስመዝገብ መጀመሩን ከፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ያገኘነው መረጃ አመለከተ። "አደይ አበባ" የኢዴፓ የምርጫ ምልክት ሆኖ ተመረጠየኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች ሲጠቀምበት የነበረውን የሁለት ጣቶችን ምስል የያዘ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት እንዲለውጥ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተሰጠው ውሳኔ መሰረት ለውጥ ማድረጉን ከፓርቲው ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ። ኢዴፓ የስም ለውጥ ሰርተፊኬቱን ከምርጫ ቦርድ ተቀበለ
ቀደም ሲል “ኢዴአፓ - መድህን” በሚል ስያሜ ይጠራ የነበረው ፓርቲ ባለፈው ዓመት በጥር ወር ባካሄደው አራተኛ ድርጅታዊ ጠቅላላ ጉባዔ የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ በማድረግ ፓርቲው፤ “የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)” በሚል ስያሜ እንዲጠራ የስም ለውጥ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።
Read more...
|
|
|
| Page 1 of 10 |







