“ምፅዋት የተነፈገ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል”
(ከአብዱራህማን አህመዲን - በግል)
ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነኝ ረቡዕ ጥቅምት 25 ቀን 2002 ዓ.ም በአምስተኛ ዓመት ቁጥር 217 በወጣው የሰንደቅ ጋዜጣ እትም በገጽ 5 እና 14 ላይ አቶ ገብሩ አስራት የሰጡት ቃለ ምልልስ ነው፡፡ የአቶ ገብሩ ቃለ ምልልስ እኔንም ሆነ በአመራር አባልነት የምገኝበትን ፓርቲ (ኢዴፓን) በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚያወሳበት ሁኔታ ስላለ ይህንን ጽሑፍ ለማዘጋጀት ምክንያት ሆኖኛል፡፡ ወደ ጽሑፌ መሰረታዊ ጉዳይ ከማምራቴ በፊት ሁለት ማሳሰቢያዎችን ላስቀድም፡፡












