|
ኢዴፓ ዓርብ እለት በመቀሌ ስብሰባ ያካሂዳል |
|
|
Monday, 10 May 2010 23:33 |
የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ዓርብ ግንቦት 6 ቀን 2002 ዓ.ም በመቀሌ ከተማ ሕዝባዊ ስብሰባ እንደሚያካሂድ ከፓርቲው ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ።
የምረጡኝ ቅስቀሳ የሚደረግበት ጊዜ ከመጠናቀቁ በፊት ሕዝባዊ ስብሰባ ለማካሄድ በእቅድ ከያዛቸው አካባቢዎች መካከል አንዱ መቀሌ መሆኑን ጽ/ቤቱ ጠቅሶ፣ ስብሰባውን የተሳካ ለማድረግ በስፍራው የሚገኙ አባላት ቅድመ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ላይ መሆናቸውን ጨምሮ ገልጿል።
በዚሁ መሰረት፣ ስብሰባው የሚካሄድበትን ቀን በመግለጽ አዳራሽ ለማግኘት ለክልሉ የመንግስት አካላት ደብዳቤ የተጻፈ መሆኑን ጽ/ቤቱ ገልፆ፤ ይህንኑ ስራ ለማስተባበርና የቅስቀሳ ስራውን ለማከናወን በአቶ ነፃነት ደመላሽ የተመራ ቡድን ወደ ስፍራው መንቀሳቀሱን አመልክቷል።
|