የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በግንቦት ወር 2002 ዓ.ም በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ውድድር በዋናነት የሚያነሳቸውን የመከራከሪያ አጀንዳዎች፣ ፖሊሲዎችና ስልቶች የያዘ የምርጫ ማንፌስቶ በመጪው ማክሰኞ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ከፓርቲው ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ።
የኢዴፓ የምርጫ ማንፌስቶ ማክሰኞ ይፋ ይሆናል
የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በግንቦት ወር 2002 ዓ.ም በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ውድድር በዋናነት የሚያነሳቸውን የመከራከሪያ አጀንዳዎች፣ ፖሊሲዎችና ስልቶች የያዘ የምርጫ ማንፌስቶ በመጪው ማክሰኞ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ከፓርቲው ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ።
Read more...
ዛሬም ይቻላል!!!መጽሐፉ ተመረቀ፤ “መድሎት” ማለት “መመዘኛ፣ ሚዛን” ማለት ነውየኢዴፓ ሊቀመንበር አቶ ልደቱ አያሌው “መድሎት” በሚል ርዕስ ያዘጋጁት የሀገሪቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች የሚዳስስ መጽሐፍ ረቡዕ የካቲት 10 ቀን 2002 ዓ.ም በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል መመረቁን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። ባለፈው ሳምንት መጠናቀቂያ አካባቢ የወጡ የአገር ውስጥ ጋዜጦች “አወዛጋቢው አቶ ልደቱ አነጋጋሪ መጽሐፍ ጻፉ” በሚል ርዕስ ጭምር በፊት ለፊት ገፆቻቸው የተለያዩ ዘገባዎችንና አስተያየቶችን መጻፋቸውን የዜና ምንጩ ጠቅሶ፤ በመጽሐፉ ምረቃ ስነ ስርዓት ላይ በርካታ ጋዜጠኞች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ደራሲያን፣ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና ታዋቂ ግለሰቦች መገኘታቸውን አስታውቋል። የመጀመሪያው የፓርቲዎች ክርክር ሳይቆራረጥ መቅረቡ ታወቀ
በመጪው ግንቦት ወር አጋማሽ ላይ ለሚደረገው አገር አቀፍ ምርጫ፣ የካቲት 5 ቀን 2002 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስቱዲዮ ተቀርፆ የተላለፈው የፓርቲዎች ክርክር ምንም ዓይነት ሳንሱር ሳይደረግበት የቀረበ መሆኑን ከኢዴፓ ጸ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ።
Read more...
በኢዴፓ ሊቀመንበር የተዘጋጀ መጽሐፍ ታተመ በኢዴፓ ሊቀመንበር በአቶ ልደቱ አያሌው የተዘጋጀ መጽሐፍ ታትሞ የካቲት 11 ቀን 2002 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል የሚመረቅ መሆኑን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። በሁለት ዋና ዋና ክፍሎችና በበርካታ ምዕራፎች የተዘጋጀው ይኸው መጸሐፍ፣ ከአምስት መቶ በላይ ገፆች ያሉት መሆኑን የዜና ምንጩ ገልጿል።መጸሐፉ “መድሎት” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መሆኑን የዜና ምንጩ ጠቅሶ፣ ህትመቱ የተጠናቀቀ በመሆኑ በመጪው ረቡዕ በሚደረገው የምረቃ ሥነ-ስርዓት ላይ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ይጠበቃል ሲል አስታውቋል። |
|
|
| Page 2 of 12 |








