የኢዴፓ አመራር፤ ከቀኝ ወደ ግራ ሙሼ፣ መስፍን፣ ልደቱ፣ አብዱራህማን፣ ደረጀና ሙጬ፣ ከድርድርና ከፊርማ በኋላ
|
የኢዴፓ አመራር፤ ከቀኝ ወደ ግራ ሙሼ፣ መስፍን፣ ልደቱ፣ አብዱራህማን፣ ደረጀና ሙጬ፣ ከድርድርና ከፊርማ በኋላ
የኢዴፓ አመራር ከአውሮጳ አምባሳደሮች ቡድን ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያየ
የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) አመራር አባላት ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ ከተማ ከሆኑ የአውሮጳ አገራት አምባሳደሮች የሰብአዊ መብትና የዴሞክራሲ ቡድን ጋር ህዳር 4 ቀን 2002 ዓ.ም ከቀትር በኋላ መነጋገራቸውን ከፓርቲው ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ፡፡
Read more...
ኢዴፓ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለምርጫው ያለውን ዝግጅት ገለጸ፤ መድረክ ከኢዴፓ ላይ እጁን እንዲሰበስብ አሳሰበ
የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ዛሬ ከቀትር በኋላ በግዮን ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ “ምርጫው የሕዝቡ ትክክለኛ ውሳኔ የሚከበርበት፣ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሊሆን ይገባል” ሲል አሳሰበ፡፡ ጋዜጣዊ መግለጫው በዋናነት ያተኮረው በግንቦት ወር 2002 ዓ.ም የሚካሄደውን አገራዊና ክልላዊ ምርጫ በተመለከተ ሲሆነ፤ ከገዥው ፓርቲ ጋር ስለተደረገው ድርድርና ስለተገኘው ውጤትም ጠቅሷል፡፡ ኢዴፓ ነገ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል
የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ሐሙስ ህዳር 3 ቀን 2002 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት በግዮን ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ከፓርቲው ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ፡፡
Read more...
ኢዴፓ የምርጫ ዝግጅቱን አጠናክሮ ቀጥሏልተወናብደው የነበሩ አባላቱም እየተመለሱ ነው የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ ከሀገሪቱ የቆዳ ስፋት ሰባ አምስት በመቶ (75%) በሚሆነው አካባቢ ዕጩዎችን ለማቅረብ የጀመረውን ዝግጅት አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፤ ከምርጫ 97 በኋላ በሀገሪቱ በተፈጠረው ፖለቲካዊ ሁኔታና በፓርቲው ላይ በተነዛው መጠነ ሰፊ የአሉባልታ ዘመቻ ምክንያት ተወናብደው ከፓርቲያቸው ተነጥለው የነበሩ አባላትም በጊዜ ሂደት ሀቁን በመገንዘባቸው በጊዜአዊነት ተጠግተዋቸው ከነበሩ ፓርቲዎች በመልቀቅ ወደ እናት ፓርቲያቸው እየተመለሱ መሆኑን የኢዴፓ ማዕከላዊ ምክር ቤት አባልና የድርጅት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሊቀ መንበር የሆኑት አቶ ነፃነት ደመላሽ አስታወቁ፡፡ |
|
|
| Page 5 of 12 |








