ለሁለት ወራት ያህል ተደራድረው የሥምምነት ሰነዶችን በፊርማቸው ያጸደቁት አራቱ ፓርቲዎች (ማለትም፤ ኢዴፓ፣ ቅንጅት፣ መኢአድና ኢህአዴግ) በቀጣይነት ሊደራደሩባቸው ከመረጧቸው አጀንዳዎች መካከል፤ “በፖለቲካ አመለካከታቸው ምክንያት የታሰሩ፣ ከሥራና ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ፣ ዛቻ ማስፈራራትና እገታ የደረሰባቸው እና በተለያዩ ክሶች በየፍርድ ቤቱ የሚመላለሱ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትንና ደጋፊዎችን በተመለከተ” በሚለው አጀንዳ ላይ ቀጣይ ድርድር መጀመራቸውን ከኢዴፓ የውጭ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ አመለከተ፡፡












